1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የሐምሌ 24 ቀን 2017 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleቅዳሜ፣ ነሐሴ 24 2017

በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ ከሐምሌ ወዲህ ቢያንስ በ125,000 ሰዎች ላይ ጉዳት አደረሰ። የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ የሊቢያን ቀውስ ለማብቃት የተባበሩት መንግሥታት ላዘጋጀው ፍኖተ-ካርታ ድጋፋቸውን ገለጹ። የየመን ጠቅላይ ሚኒስትር እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት በዚህ ሣምንት እስራኤል በፈጸመችው ጥቃት ተገደሉ። አሜሪካ በመስከረም በሚካሔደው የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባኤ የፍልስጤም አስተዳደር ፕሬዝደንት ማሕሙድ አባስ እንዲሳተፉ እንደማትፈቅድ አስታወቀች። የዩክሬን ምክር ቤት የቀድሞ አፈ-ጉባኤ አንድሬ ፓሩቢ በልቪቭ ከተማ በጥይት ተመተው ተገደሉ።

https://p.dw.com/p/4zkQT
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።