1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የጀርመን የምርጫ ስርዓትና የኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች የጀርመን ጉብኝት

ማክሰኞ፣ መጋቢት 8 2018

ከኢትዮጵያ ፣ የተለያዩ መገናኛና ብዙሀን የተውጣጡት ጋዜጠኞች በመጪው እሁድ የአካባቢ ምርጫ በሚካሄድበት በጀርመንኛ መጠሪያው በራይንላንድ ፋይልስ በእንግሊዘኛው በራይንላንድ ፕላቲኔት ፌዴራዊ ግዛት ዋና ከተማ ማይንዝ ተገኝተው የምርጫ ሂደቱን፣ የምርጫ ዘመቻዎችንና ፣የቴሌቪዥን ክርክርም በአካል ተገኝተው ተከታትለዋል።

https://p.dw.com/p/5AZLW
Deutschland Berlin 2026 | Gebäude des Deutschen Bundestages
ምስል፦ Solomon Muche/DW

የጀርመን የምርጫ ስርዓትና የኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች የጀርመን ጉብኝት

ከጥቂት ወራት በኋላምርጫከምታካሂደው ከኢትዮጵያ የተለያዩ መገናኛና ብዙሀን የተውጣጡ ጋዜጠኞች ፣ባለፈው ሳምንት እዚህ ጀርመን ስለሀገሪቱ የምርጫ ሂደት ግንዛቤ ማስጨበጫ ጉብኝት አድርገዋል። በፌደራል ጀርመን የምርጫ ስርዓቶች እና አተገባበር ላይ ባተኮረው በዚህ የአንድ ሳምንት ጉብኝት የጀርመን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን ጨምሮ የምርጫ ጉዳይ የሚመለከታቸውን ተቋማት የጎበኙት ጋዜጠኞቹ ገለጻዎችም ተደርገውላቸዋል።

 በመጪው እሁድ የአካባቢ ምርጫ በሚካሄድበት ከ16ቱ የጀርመን ፌደራዊ ግዛቶች አንዱ በሆነው በጀርመንኛ መጠሪያው በራይንላንድ ፋልስ በእንግሊዘኛው በራይንላንድ ፕላቲኔት ፌዴራዊ ግዛት ዋና ከተማ ማይንዝም የምርጫ ሂደቱን፣ የምርጫ ዘመቻዎችንና ፣የቴሌቪዥን ክርክርም በአካል ተገኝተው ተከታትለዋል።

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ባለፈው ሳምንት የጎበኙት ማይንዝ የሚገኘው የጉትንበርግ ቤተ መዘክር
የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ባለፈው ሳምንት የጎበኙት ማይንዝ የሚገኘው የጉትንበርግ ቤተ መዘክር ምስል፦ Solomon Muchie/DW

ጋዜጠኞቹ በበርሊንና በማይንዝ ከተሞች ቆይታቸው ታሪካዊ ቦታዎችንና ቤተ መዘክሮችንም ጎብኝተዋል። በዛሬው አውሮጳና ጀርመን ዝግጅታችን ኂሩት መለሰ ከጋዘጠኞቹ ጋር በጉብኝቱ የተካፈለውን የአዲስ አበባውን የዶቼቬለ ዘጋቢ ሰሎሞን ሙጬን አነጋግራዋለች። ሙሉውን ቃለ መጠይቅ ለማዳመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ

ኂሩት መለሰ

ፀሐይ ጫኔ