1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

DW Amharic የኅዳር 27 ቀን 2018 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleቅዳሜ፣ ኅዳር 27 2018

ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ መካከል “አዲስ ግጭት እንዳይቀሰቀስ መከላከል” ላይ ማተኮር እንዳለባት የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ይፋ ያደረገው የብሔራዊ ደሕንነት ፖሊሲ ሰነድ አሳየ። ኢትዮጵያ ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የማርበርግ ቫይረስ የሙከራ ክትባት መስጠት ልትጀምር ነው። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በድሮን በፈጸመው ጥቃት 33 ሕጻናትን ጨምሮ 50 ሰዎች መገደላቸውን የሐኪሞች ቡድን አስታወቀ። በደቡብ አፍሪካ በርካታ ተጠርጣሪዎች በከፈቱት ተኩስ ሕፃናትን ጨምሮ 11 ሰዎች መገደላቸውን ፖሊስ ገለጸ። የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሬድሪሽ ሜርስ ወደ እስራኤል እና ዮርዳኖስ አመሩ።

https://p.dw.com/p/54tIQ
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።