1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

DW Amharic የሰኔ 22 ቀን 2017 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleእሑድ፣ ሰኔ 22 2017

በአማራ ክልል ከተሞች በሺሕዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች የተሳተፉባቸው መንግሥትን የሚደግፉ ሰልፎች ተካሔዱ። የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ “ቁልፍ የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ አለመሆን” እና “በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ የሚደርሰውን ጫና” አወገዘ። የዩጋንዳ ፕሬዝደንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ በሚቀጥለው ዓመት በሚካሔደው ምርጫ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ። እስራኤል 12 ቀናት የዘለቀውን ውጊያ የገታውን የተኩስ አቁም ታከብራለች የሚል ዕምነት እንደሌላት ኢራን ሥጋቷን ገለጸች። የኢየሩሳሌም ፍርድ ቤት በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ላይ የቀረበውን የሙስና ክስ ለመመልከት ይዞት የነበረውን ቀጠሮ ሰረዘ።

https://p.dw.com/p/4weuw
ቀጣዩን ክፍል እለፈው ስለዚህ ዝግጅት

ስለዚህ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።