Eshete Bekeleእሑድ፣ ሰኔ 22 2017በአማራ ክልል ከተሞች በሺሕዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች የተሳተፉባቸው መንግሥትን የሚደግፉ ሰልፎች ተካሔዱ። የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ “ቁልፍ የዴሞክራሲ ተቋማት ገለልተኛ አለመሆን” እና “በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ የሚደርሰውን ጫና” አወገዘ። የዩጋንዳ ፕሬዝደንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ በሚቀጥለው ዓመት በሚካሔደው ምርጫ የመሳተፍ ፍላጎት እንዳላቸው አስታወቁ። እስራኤል 12 ቀናት የዘለቀውን ውጊያ የገታውን የተኩስ አቁም ታከብራለች የሚል ዕምነት እንደሌላት ኢራን ሥጋቷን ገለጸች። የኢየሩሳሌም ፍርድ ቤት በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ላይ የቀረበውን የሙስና ክስ ለመመልከት ይዞት የነበረውን ቀጠሮ ሰረዘ።