1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ
ኤኮኖሚሰሜን አሜሪካ

የአሜሪካና አውሮፓ የግሪንላንድ ውዝግብ ጫና ያሳደረበት የዳቮሱ አለም አቀፍ የኢኮኖሚ ጉባኤ

ገበያው ንጉሤ
ሐሙስ፣ ጥር 14 2018

ትናንት ምሽት ሳይጠ።በቅ በግሪንላንድ ጉዳይ ላይ ወደፊት አሜሪካ ዴንማርክና ኔቶ ከስምምነት ለመድረስ በሚያስችል ማዕቀፍ ላይ የተስማሙ መሆኑን እራሳቸው ፕሬዝዳንት ትራምፕ በማህበራዊ ገጻቸው ማስታወቃቸው ለብዙዎች እፎይታን አስገኝቷል።ከዚሁ ጋርም ጀርመንን ፈረንሳይንና ብርታኒያን ጨምሮ በስምንት አገሮች ላይም የዛቱትን ታሪፍ እንደማይጥሉም ገልጸዋል።

https://p.dw.com/p/57FiU
Schweiz Davos 2026 | US-Präsident Donald Trump spricht beim Weltwirtschaftsforum in Davos
ምስል፦ Fabrice Coffrini/AFP/Getty Images

የአሜሪካና አውሮፓ የግሪንላንድ ውዝግብ ጫና ያሳደረበት የዳቮሱ ዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ጉባኤ

በፕሬዝዳንት ትራምፕ የግሪንላንድ ጥያቄ ላይ የተነሳው ክርክርና ተቃውሞ

ፕሬዝዳንት ትራም ቀደም ሲል ግርንላንድ ለአሜርካ ደህንነት ወሳኝ በመሆኗ  የአሜሪካ ግዛት  አካል መሆን አለባት በማለት እንድትሰጣቸው፤ ካልሆነም በማናቸውም አማራጭ የአሜርካ አካል መሆኗ እንደማይቀር ሲገልጹ ቆይተዋል። የአዎርፓና የኔቶ አባል መንግስታት ግን ይህ የሬዝዳንት ትራም አቋም የኔቶን ህግ የሚጥስና የአትላንቲክ ማዶና ማዶ ግንኑነትን የሚያፈርስ ነው በማለት ተቃውሟቸውን ከመግለጽ በተጨማሪ፤ የተወሰኑ አገሮች  ወደ ግሪንላንድ ወታደሮችን በመላክ ጭምር ለዴንማርክ አጋርነታቸውን ገልጸዋል። ሆኖም ግን ትራም ከነዚህ አገሮች ወደ አሜሪካ በሚገቡ ሸቀጦች ላይ የተጨማሪ ታክስ ውሳኔ በማስተላለፍ የግሪንላድ የይገባኛል ጥያቄያቸው የማይቀለበስ መሆኑን ነው የገለጹት። በዳቮሱ የምጣኔ ሀብት ጉባኤ ተገንተውም ይህንኑ ጥያቄያቸውን አስተጋበተዋል።  

ተደረሰበት የተባለው ያልተጠበቀ ስምምነት

ፕሬዝዳንቱ በጉባኤው ባሰሙት ዘለግ ያለ ንግግራቸውየህብረቱና የኒቶ አባል አገራትመሪዎችን ወርፈዋል፤ አውሮፓን ባጠቃይም በአቅመቢስነት ፈርጀዋል፤። ምሽት ላይ ግን ባልተጠበቀ ሁኔታ በአዋዛጋቢው ግሪንላንድ ላይ ወደፊት አሜሪካ ዴንማርክና ኔቶ ከስምምነት ለመድረስ በሚያስችል ማዕቀፍ ላይ የተስማሙ መሆኑን እራሳቸው ፕሬዝዳንት ትራም በማህበራዊ ገጻቸው ማስታወቃቸው ለብዙዎች እፎይታን አስገኝቷል።  ፕሬዝዳንቱ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጀርመንን ፈረንሳይንና ብርታኒያን ጨምሮ በስምንት አገሮች ላይ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ሊጥሉት የነበረውን ታሪፍም ተግባራዊ እንደማይደርጉ አስታውቀዋል።

የስምምነቱ ይዘት

ትራምፕ ከዚህ ውሳኔ የደረሱት ከኔቶ ዋና ጸሀፊ ሚስተር ማርክ ሩተ ጋር ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ መሆኑ ታውቋል። ማርክ ሩተ ዛሬ ክፕረዝዳንት ትሩምፕ ጋር ያደረጉትን ውይይት ይዘት ሲገልጹ” ትናንት ያደረግነው ውይይት በጣም ጠቃሚና ባጠቃላይም የኔቶ አገሮችና አሜርካ ጭምር የአርክቲክ አካባቢ ከሩሲያና ቻይና ስጋት ነጻ ስለሚሆንበት ነው” በማለት በግሪንላንድም ቻይናና ሩሲያ ምንም አይነት የኢኮኖሚና ወታደራዊ እንቅሳቅሴ እንዳይኖራቸው ማድረግ  ላይ ያተኮረ እንደህነ ገልጸዋል። ፕሬዝዳን ትራምፕም ስምምነቱ የረጅም ግዜ ሂደት እንደሆነ አስታውሰው የኔቶ ዲነማርክና አሜርካ  ሉካን ውይይት እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል ።

የዳቮሱ ጉባኤ ተሳታፊዎች ቲምኮክ፣የንሰን ሁአንግ፣ ክርስቲን ላጋርድ
የዳቮሱ ጉባኤ ተሳታፊዎች ቲምኮክ፣የንሰን ሁአንግ፣ ክርስቲን ላጋርድ ምስል፦ Jonathan Ernst/REUTERS

ስምምነቱ የፈጠረው የዕፎይታ ስሜት

የአውሮፓና የስሜን አትላንቲክ አገሮች ባጠቃላይ ሲስማሙ የተስማሙበት የግሪናልድ ጉዳይ ግልጽ ባይሆንም ጥያቄው ግን ከሀይል መልስ በውይይትና ድርድር እንዲመለስ ከስምምነት መደረሱ ባውሮፓና የነኔቶ ባል አመንግስታት ዘንድ ኧፎይታን አስገኝቷል። የተነቃነቀውን የኔቶና የአውሮፓና አሜርካ ግንኑነትንም ከመፈርስ ያዳነ ተደርጎ ተወስዷል። ሆኖም ግን የተፈጠረው ክስትት በተለይ ያውሮፓና አሜርካ ግንኙነት ላይ ጠባሳ ትቶ እንደሚያልፍ ነው በብዙዎች የሚነገረው።  በጀርመን ቤርቴልስማን ስቲፈንግ የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የፖለቲካ ተንታኝ የሆኑት ብራንዶን ቦህን ስምምነቱ  “ እ እ እ በ1951 ም ጀርመና ዴማርክ የደርሱበትን የመካለክያ ስምምነት ላይ እንደገና ለመደራደር ያለመ ነው። ይህን ከዚህ ሁሉ ሳይደረስ ማድረግ ይቻል ነበር” በማለት የደረሰው ጉዳት  ቀላል እንዳልሆነ ገልጸዋል።

የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሪድሪሽ ሜርስ በዳቮሱ ጉባኤ
የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሪድሪሽ ሜርስ በዳቮሱ ጉባኤምስል፦ Fabrice Coffrini/AFP/Getty Images

አሸናፊና ተሸናፊ

በዚህ ተደረሰ  በተባለው ስምምነት አሸናፊው ማን ሊሆን እንደሚችል ተጠይቀው ሲመልሱም፤ “  የአሜሪካ ፍላጎት በአርክቲክ ክልል ወታደራዊ ይዞታ እንዲኖራት ነው፤ በዚህ በኩል ተሳክቶላት ሊሆን ይችላል።  ግን ይህ ስምምነት ቀደም ሲል የነበረ በመሆኑ አዲስ ነገር የለውም። በአውሮፓውያን በኩልም እንደ ድል ሊወሰድ ይችላል፤ ምክኒያቱም አውሮፓውያን ክተባበሩና ከጸኑ የሚደርስባቸውን ማናቸውንም ጫና መቆቁቋም  እንደሚችሉ አሳይተዋል” ብለዋል።
ዛሬ ማምሻውን እዚህ ብራስልስ በመካሄድ ላይ ያለው ያአውሮፓ ህብረት የመሪዎች አስቸኳይ ጉባኤም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቀለበሱት የተባለው የግሪንላድ ጥያቄ ቀጣይ ሂደት ላይና ሊሎች አጣዳፊ አጅንዳዎች ላይ  ውሳኔ አሳልፎ ይነሳል ተብሎ ይጠበቃል

ገበያው ንጉሴ
ኂሩት መለሰ
እሸቴ በቀለ