ሐሙስ፣ ሚያዝያ 8 2018በአማራ ክልል ራያ ቆቦ ወረዳ በጸበል ቦታ በደረሰ ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ 8 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። በአደጋው ከ30 በላይ ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም። የአዲስ ስታንዳርድ የበይነ መረብ መገናኛ ብዙኃን ማኔጂንግ ኤዲተር ትላንት ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ከሥራ ገበታው ከተወሰደ በኋላ ዛሬም የደረሰበት አልታወቀም። ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ሁለት የፖሊስ መኮንኖች እና አንድ የመከላከያ ሠራዊት አባል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በታጣቂዎች ተገድለዋል። በዛሬው ዜና መጽሔት ከሚቀርቡ ዘገባዎች መካከል እነዚህ ይገኙበታል።