«ፈረንሳይ በኢትዮጵያ እና በምስራቅ አፍሪቃ ሀገራት ላይ የምታደርገውን ጣልቃ ገብነት ታቁም»
ቅዳሜ፣ ኅዳር 25 2014ማስታወቂያ
በፈረንሳይ የተለያዩ ከተሞች ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን ትውልደ ኢትዮጵያውያን ፣ኤርትራውያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች ምዕራባውያን ሀገራት በተለይ ፈረንሳይ በኢትዮጵያ ላይ ታሳድራለች ያሉትን ግፊትና ጫና እንዲሁም ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሀን ያሰራጫሉ ያሏቸውን የሀሰት ዜና በመቃወም ዛሬ ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል። ፈረንሳይ በኢትዮጵያ እና በምስራቅ አፍሪቃ ሀገራት ላይ የምታደርገውን ጣልቃ ገብነት ታቁም ፤ የፈረንሳይን ጨምሮ ዓለማቀፍ የመገናኛ ብዙኃን በኢትዮጵያ ላይ የሚያደርትን የተሳሳተ ዘገባ ያቁሙ የሚሉ መልዕክቶች ተላልፈውበታል።
ኃይማኖት ጥሩነህ
ታምራት ዲንሳ