140 ኪሎግራም ካናቢስ ተቃጠለ
ዓርብ፣ ጳጉሜን 1 2011ማስታወቂያ
የድሬዳዋ ፖሊስ ከከተማይቱ የያዘውን በርከት ያለ ካናቢስ የተባለ አደንዛዥ እጽ ዛሬ አቃጠለ።ፖሊስ እንዳለው ይኽው ከ140 ኪግራም በላይ የሚመዝነው ካናቢስ በከተማዋ ቢሰራጭ ኖሮ ብዙ ወጣቶች በአደንዛዥ እጹ ተጽእኖ ስር ሊወድቁ ይችሉ ነበር።እደንዛዥ እጹ ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ድሬዳዋ እንደሚመጣ ያሳወቀው ፖሊስ የእጹን ዝውውር ለመከላከል ጥረቱን አጠናክሮ መቀጠሉን ተናግሯል።ችግሩን ከምንጩ ለማስወገድ እሰራለሁም ብሏል።ዝርዝሩን የድሬዳዋው ወኪላችን መሳይ ተክሉ ልኮልናል።
መሳይ ተክሉ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ