1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፖለቲከኞች ጦር ግንባር የመዝመት ውሳኔ 

ረቡዕ፣ ኅዳር 15 2014

ከፍተኛ አመራሮቹን ጨምሮ አባላትና ደጋፊዎቹ ወደ ጦር ግንባር እንዲዘምቱ ትናንት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የወሰነው ኢዜማ የፖለቲካ አመለካከት ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው እንዲህ ባለው ጊዜ ለሀገር ህልውና በጋራ መቆም ምርጫ የሌለው ግዴታ ነው ብሏል።

https://p.dw.com/p/43QIy
EZEMA Partei Äthiopien Addis Abeba
ምስል Yohannes G/Egziabher/DW

የፖለቲከኞች ጦር ግንባር የመዝመት ውሳኔ 

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደ ጦር ግንባር መሄድ  የኢትዮጵያን ድል ያፋጥናል ብሎ እንደሚያምን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትሕ ( ኢዜማ ) ተናገረ።  ከፍተኛ አመራሮቹን ጨምሮ አባላትና ደጋፊዎቹ ወደ ጦር ግንባር እንዲዘምቱ ትናንት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የወሰነው ኢዜማ የፖለቲካ አመለካከት ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው እንዲህ ባለው ጊዜ ለሀገር ህልውና በጋራ መቆም ምርጫ የሌለው ግዴታ ነው ብሏል።አንድ የፖለቲካ ሳይንስ አዋቂ በበኩላቸው የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በጦርነት ለመጨረስ ያስገደደው ያቀረበው የሰላም አማራጭ ተቀባይነት አለማግኘቱና የተወሰኑ ምዕራባውያን ሃገራት ጦርነቱን ቀጣናዊ ለማድረግ ጣልቃ መግባታቸው ነው ብለዋል።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ