1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 የፍርድ ቤቱን ዉሳኔ ታገደ

ዓርብ፣ ነሐሴ 22 2012

ባለፈዉ ሰኔ በተቀሰቀሰዉ ሁከትና ግጭት ተጠርጥረዉ የታሰሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ ባለሥልጣን ደጀኔ ጣፋ እና 3 የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ (OMN) ጋዜጠኞች እያንዳዳቸዉ በ10 ሺሕ ብር ዋስትና እንዲለቀቁ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ችሎት ባለፈዉ ሰኞ ወስኖ ነበር

https://p.dw.com/p/3heYz
Deutschland Äthiopiens Oromo federalist congress |  Dejene Taffa
ምስል Eshete Bekele Tekele/DW

የፍርድ ቤት ዉሳኔና የአቃቤ ሕግ ተቃዉሞ

የኢትዮጵያ የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በዋስ እንዲለቀቁ የወሰነላቸዉ ተጠርጣሪዎች እንዳይለቀቁ አቃቤ ሕግ  በመቃወሙ የፍርድ ቤቱ ዉሳኔ ገቢር ሳይሆን ቀረ።ባለፈዉ ሰኔ በተቀሰቀሰዉ ሁከትና ግጭት ተጠርጥረዉ የታሰሩት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ ባለሥልጣን ደጀኔ ጣፋ እና 3 የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ (OMN) ጋዜጠኞች እያንዳዳቸዉ በ10 ሺሕ ብር ዋስትና እንዲለቀቁ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ችሎት ባለፈዉ ሰኞ ወስኖ ነበር።ይሁንና አቃቤ ሕግ ይግባኝ በመጠየቁ የፍርድ ቤቱ ዉሳኔ አልተከበረም።የአቶ ደጀኔ ጠበቃ የፍርድ ቤቱ ዉሳኔ መሻሩን  ይቃወማሉ።

ስዩም ጌቱ

ነጋሽ መሐመድ

እሸቱ በቀለ