1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፌደሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል ምርጫን አስመልክቶ ውሳኔ አሳለፈ

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 30 2012

የፌደሬሽን ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምርጫን በሚመለከት እያደረገ ባለው እንቅስቃሴ ላይ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ ክልሉ ያወጣው የምርጫ አዋጅ ከሕገ መንግሥት እንደሚቃረን ፣ የምርጫ ኮሚሽን ማቋቋሙ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠውን ስልጣን የሚጥስ መሆኑን ወስኗል።

https://p.dw.com/p/3i34D
Äthiopien | Logo der Tigray Wahlkommission
ምስል DW/M. Hailesilasie

የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ እና ውሳኔዎቹ

የፌደሬሽን ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባው የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ምርጫን በሚመለከት እያደረገ ባለው እንቅስቃሴ ላይ ውሳኔ አሳልፏል።
ምክር ቤቱ ክልሉ ያወጣው የምርጫ አዋጅ ከሕገ መንግሥት እንደሚቃረን ፣ የምርጫ ኮሚሽን ማቋቋሙ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠውን ስልጣን የሚጥስ መሆኑን ወስኗል።
የክልሉ ምክር ቤት አስፈፃሚ አካላት እና የምርጫ ኮሚሽን ምርጫን በሚመለከት ያወጣው የምርጫ አዋጅ ያስተላለፏቸው ውሳኔዎች እና የፈፀሟቸው ተግባራት ከሕገ መንግስት ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው እንዳልተደረጉ የሚቆጠሩ ፣ የማይፀኑ እና ተፈፃሚነት የሌላቸው ናቸው በማለት የፌደሬሽን ምክር ቤት ወስኗል።

ሰለሞን ሙጬ

ታምራት ዲንሳ