1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ዘገባ

ማክሰኞ፣ ጥር 19 2012

ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ብርሐኑ ፀጋዬ ዛሬ ለሕዝብ ተዋካዮች ምክር ቤት የ6 ወራት ዘገባ ሲያቀርቡ እንዳሉት በስም ያልጠቀሷቸዉ የክልል መንግስታት ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ ለመስጠት ፈቃደኞች አይደሉም።

https://p.dw.com/p/3WuiT
Äthiopien Addis Abeba Birehanu Tsegaye
ምስል DW/Y. G. Egziabher

ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ ክልሎችን ወቀሱ

የኢትዮጵያ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በየክልሉ የሚገኙ ተጠርጣሪዎች ለፍርድ ለማቅረብ ለሚያደርገዉ ጥረት የክልል መንግሥታት ባለመተባበራቸዉ ጥረቱ መታጎሉን አስታወቀ።የፌደራሉ ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ብርሐኑ ፀጋዬ ዛሬ ለሕዝብ ተዋካዮች ምክር ቤት የ6 ወራት ዘገባ ሲያቀርቡ እንዳሉት በስም ያልጠቀሷቸዉ የክልል መንግስታት ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ ለመስጠት ፈቃደኞች አይደሉም።ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ እንደዘረዘሩት በተጠርጣሪዎች ብዛት በኒ ሻንጉል ጉሙዝ፣ደቡብ ኢትዮጵያና ኦሮሚያ መስተዳድሮች ከአንድ እስከ ሶስት ያለዉን ደረጃ ይይዛሉ።

ዮሐንስ ገብረ እግዚአብሔር 

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ