የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 6 2013ማስታወቂያ
የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት የፕረስ ሴክረተሪ ቢልለኔ ሥዩም ዛሬ ከቀትር በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት አጠር ያለመግለጫ አራት ዐበይት ጉዳዮችን አንስተው አብራርተዋል ከጋዜጠኞችም ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጥተዋል። በዛሬው መግለጫ ከተነሱ ነጥቦች መካከል፦ የሲቪሎች አፋር ክልል ውስጥ መገደል፣ በሰሜን የኢትዮጵያ ክፍል ስላለው የሰብአዊ ርዳታ አቅርቦት፣ ከትናንት በስትያ በመንግስት ስለተላለፈው ብሔራዊ ጥሪ እንዲሁም ስለ ሕወሃት እና ሸኔ ተደረገ ስለተባለው ትብብር አብራርተዋል። መግለጫውን የአዲስ አበባው ወኪላችን ሰለሞን ሙጬ ተከታትሎ ቀጣዩን ዘገባ ልኮልናል።
ሰለሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ