የጠ/ሚ ዐቢይ በፍቅር የመደመር ጉዞ አውሮጳ
ሰኞ፣ ጥቅምት 12 2011ማስታወቂያ
በሌላ በኩል የጠቅላይ ሚኒስትሩን መምጣት በጉጉት ብንጠብቅም ላለፉት 27 ዓመታት በኢትዮጵያ ሲፈጸም የነበረውን የመብት ረገጣ የዲሞክራሲ እጦት እና አፈና በመቃወም አሁን ለመጣው ለውጥ የበኩላችንን እገዛ ስናበረክት የቆየን በአቀባበሉ ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ውስጥ የበኩላችንን ተሳትፎ እንዳናደርግ ዕድል ተነፍጎናል ፤ ዲያስፖራውን ሲከፋፍሉ የነበሩ ግለሰቦች በኮሚቴው ውስጥ መካተታቸውም በአገሪቱ የተጀመረውን በፍቅር የመደመር ጉዞ መርህ እንዳያሰናክሉት ስጋት አለን ሲሉ ቅሬታቸውን የሚያሰሙ አሉ። የኢትዮጵያ ኤምባሲ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት ጄኔራል አቶ ምህረተዓብ ሙሉጌታ እና የዝግጅቱ ጊዜያዊ ኮሚቴ የሚድያ እና ሕዝብ ግንኙነት አስተባባሪ አቶ ዘለዓለም ደበበ በበኩላቸው ቅሬታው አስተባብለዋል:: ዝርዝሩን እንዳልካቸው ፈቃደ አጠናቅሮታል::
እንዳልካቸው ፈቃደ
ሸዋዬ ለገሠ
አርያም ተክሌ