የጎሮ-አዲስ አበባ ነዋሪ ስሞታ
ረቡዕ፣ መስከረም 16 2011ማስታወቂያ
አዲስ አበባ ዉስጥ በልማዱ ጎሮ ተብሎ የሚጠራዉ አካባቢ ነዋሪዎች የሚፈፀምባቸዉ ዘረፋ እና ድብደባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ መምጣቱን አስታወቁ።ሰሞኑን ከጥቃት ያመለጡ አንድ የአካባቢዉ ነዋሪ እንዳሉት በቡድን የተሰበሰቡ ወጣቶች በተለይ ማታ በየመንገዱ ዳርቻ እያደፈጡ ወደየቤቱ የሚገባዉን ነዋሪ ያጠቃሉ፤ ይዘርፋሉም።የአካባቢዉ ፖሊስም በነዋሪዎች ላይ የሚፈፀመዉ ድብደባ እና ዘረፋ መደጋገሙን አረጋግጧል።የአካባቢዉ ፖሊስ አዛዥ እንዳሉት የመንገድ ዳር መብራቶች አለሞኖር እና የሰዉ ኃይል እጥረት የፖሊስን የቁጥጥር ሥራ አስቸጋሪ አድርጎታል።
ዳግማዊ ሲሳይ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሰ