1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግል ትምህርት ቤቶች ወርኃዊ ክፍያ ቁጥጥር በድሬደዋ

ረቡዕ፣ ነሐሴ 26 2013

በድሬደዋ የሚገኙ 68 ያህል የግል ትምህርት ቤቶች በወርሀዊ ክፍያ ላይ ያደረጉት የዋጋ ጭማሪ የተጋነነ በመሆኑ ጥናት በማድረግ የክፍያ ተመን መውጣቱን የአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

https://p.dw.com/p/3zmlG
Stadt Dire Dawa in Äthiopien
ምስል Hailegzi Mehari

«መቶ በመቶ የደረሰ የግል ትምህርት ቤቶች የክፍያ ጭማሪ መኖሩ ይነገራል»

በድሬደዋ የሚገኙ 68 ያህል የግል ትምህርት ቤቶች በወርሀዊ ክፍያ ላይ ያደረጉት የዋጋ ጭማሪ የተጋነነ በመሆኑ ጥናት በማድረግ የክፍያ ተመን መውጣቱን የአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ። በዚህ ውሳኔ መሰረት ማንኛውም የግል ትምህርት ቤት  በወርሀ ክፍያ ላይ 30 በመቶ እንዲሁም  ለመመዝገቢያ ክፍያ ከ25 በመቶ በላይ ማስከፈል እንደማይችሉ ገልጿል። የኅብረተሰቡ ገቢ ለውጥ ባላመጣበት በአስተዳደሩ የተጨመረው ጭማሪ ተመንም ቢሆን አግባብ ባይሆንም በአንፃሩ የተሻለ ውሳኔ በመሆኑ አተገባበሩ ላይ ቁጥጥር እንዲደረግ ወላጆች ጠይቀዋል።

መሳይ ተክሉ

ሸዋዬ ለገሠ

ኂሩት መለሰ