የጅቡቲ እና የኢትዮጵያ ስምምነት
ሰኞ፣ ታኅሣሥ 15 2011ማስታወቂያ
ሁለቱ ሀገራት በጋራ ድንበራቸው ላይ በተለይ የእንሰሳት ሀብት ልማትን የሚጎዱ የጋራ ችግሮቻቸውን ለመፍታት ባለፈው ሰሞን የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ ድንበር ተሻጋሪ የሆኑ የእንሰሳት በሽታዎችን ለመከላከል በእንሰሳት ሀብት ዘርፍ የተሰማሩ ባለሞያዎችን እና የአርብቶ አደሩን አቅም የማጎልበት ሥራ ላይ እንደሚያተኩር የሁለቱ ሀገራት ባለሥልጣናት ተናግረዋል። መሳይ ተክሉ ከድሬዳዋ ዝርዝር ዘገባ አለው።
መሳይ ተክሉ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ