1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የድሬዳዋው ሲሳይ ዘለገሀሬ የግጥም ስራዎች

እሑድ፣ ታኅሣሥ 10 2014

"ለፍቅራችሁ" ገጣሚ ሲሳይ ከስምንት አመት በፊት ያሳተመው የግጥም መፅሀፍ ርዕስ ነበር። የዚያን ጊዜው መፅሀፍ  ከብዙዎች አስተዋውቆኛል የሚለው ሲሳይ ከዚያ በኃላ ግን መፅሀፍ ማሳተም ሀሳቡ ቢኖረውም በተለያየ ምክንያት ማሳተም አለመቻሉን አጫውቶናል።

https://p.dw.com/p/44XTv
Äthiopien | Dichter | Sisay Zelegehare
ምስል M. Teklu/DW

የገጣሚ ሲሳይ ለገሃሬ የግጥም ስራዎች ወዴት ?

ድሬደዋ ካፈራቻቸው የጥበብ ሰዎች በቀዳሚነት ስሙ የሚነሳው ገጣሚ ሲሳይ ዘለገሀሬ ከግጥም ስራዎቹ ያቀረበልን አጭር ስንኝ ነበር። የዛሬው የመዝናኛ ዝግጅታችን ከድሬደዋው ገጣሚ ጋር ያደረግነውን ጥቂት ቆይታ ይዳስሳል።

"ለፍቅራችሁ" ገጣሚ ሲሳይ ከስምንት አመት በፊት ያሳተመው የግጥም መፅሀፍ ርዕስ ነበር። የዚያን ጊዜው መፅሀፍ  ከብዙዎች አስተዋውቆኛል የሚለው ሲሳይ ከዚያ በኃላ ግን መፅሀፍ ማሳተም ሀሳቡ ቢኖረውም በተለያየ ምክንያት ማሳተም አለመቻሉን አጫውቶናል።

ከነፍስ የግጥም ስራዎች ባለፈ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚፅፋቸውን ግጥሞቹን በመድረክ በማቅረብ የብዙዎችን ቀልብ በመሳብ ይታወቃል - ሲሳይ ። ከእነዚህ መካከል እርሱም የሚያስታውሰውን "መንዳት እና መምራት" ተጠቃሽ ነው።

ሲሳይ ተወልዶ ባደገባት ድሬደዋ ስመ ጥር ከሆኑ የጥበብ ፈርጦች አንዱ ሆኖ ከተማዋን በአንድም በሌላ መልኩ በስራዎቹ ሲያስተዋውቃት ኖሯል ። እሷ ግን ያን ያክል ውለታውን እየከፈለችው ባለመሆኑ ተስፋ ወደ መቁረጡ መሄዱን ተናግሯል። 

መሳይ ተክሉ

ታምራት ዲንሳ