የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አዲስ መንግስት አቋቋመ
ረቡዕ፣ መስከረም 19 2014ማስታወቂያ
የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት እያካሄደ ባለው መስራች ጉባዔው አቶ ከድር ጁሀርን ከንቲባ አድርጎ ሾመ። የድሬ ዳዋ ከተማ አስተዳደር አዲስ መንግስት መመስረት የሚያስችለውን ጉባኤ ዛሬ አከናውኗል። በጉባዔው ወ/ሮ ፈትያ አደም የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ሆነው ለቀጣይ አምስት አመት እንዲያገለግሉ ተሹመዋል። አንድ መቶ ሰማንያ ዘጠኝ አባላት ያለውን የድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት ወ/ሮ ከሪማ አሊ በምክትል አፈ ጉባዔነት እንዱመሩ ተሹመዋል። የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤቱ እያካሄደ ባለው 3ኛ የስራ ዘመን የመጀመሪያ ዓመት 49ኛ ጉባዔው ለቀጣይ አምስት አመት የሚያገለግሉ የካቢኔ አባላትን ይፋ አድርጓል።
መሳይ ተክሉ
ታምራት ዲንሳ
አዜብ ታደሰ