የደቡብ ሱዳን ሥልጣን ማራዘሚያ ረቂቅ ሕግ እና ክርክሩ
ቅዳሜ፣ ሰኔ 30 2010ማስታወቂያ
ደቡብ ሱዳን የፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪርን የሥልጣን ለማራዘም የውሳኔ ሐሳብ አዘጋጅታለች። የአገሪቱ ምክር ቤት የውሳኔ ሐሳቡን ለማፅደቅ አንድ ወር ተሰጥቶታል። ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡ የኪርን የሥልጣን ዘመን ለማራዘም ሲባል በሕገ-መንግሥቱ ላይ ማሻሻያ ያደርጋል። ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡ ከጸደቀ የፕሬዝዳንቱ የሥልጣን ዘመን እስከ ጎርጎሮሳዊው 2021 ዓ.ም. ይራዘማል። የኪር ተቃዋሚዎች ሕጋዊ አይደለም ብለውታል። አሜሪካ በበኩሏ ረቂቁ ከተቃዋሚዎች እና ከሲቪል ማኅበረሰቡ ጋር እየተደረገ ያለውን ውይይት ይጎዳል ስትል አውግዛለች።
ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ የድምፅ ማዕቀፉን ይጫኑ
አርያም ተክሌ
እሸቴ በቀለ