1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዩናይትድ ስቴትስና የኢትዮጵያ ግንኙነት

ዓርብ፣ መስከረም 28 2014

የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ያሳድራል የሚባለዉ ጫና እዚያዉ ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንና ትዉለደ ኢትዮጵያዉያን ዘንድ ተቃዉሞም ድጋፍም ገጥሞታል

https://p.dw.com/p/41SDG
David H. Shinn, ehemaliger U.S.-Botschafter in Äthiopien
ምስል Privat

የአሜሪካ መርሕና የኢትዮጵያዉያን አሜሪካዉያን አስተያየት

የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ያሳድራል የሚባለዉ ጫና እዚያዉ ዩናይትድ ስቴትስ ዉስጥ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንና ትዉለደ ኢትዮጵያዉያን ዘንድ ተቃዉሞም ድጋፍም ገጥሞታል።የኢትዮጵያዉያን አሜሪካዉያን ሲቢል ምክር ቤት የተባለዉ ማሕበር ሰብሳቢ ዲያቆን ዮሴፍ ተፈሪ የአሜሪካን መንግስትን ርምጃ እንደሚቃወም ለተለያዩ የሐገሪቱ መስሪያ ቤቶች በፃፈዉ ደብዳቤ አስታዉቋል።የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ደምፅ የተሰኘዉ ንቅናቄ ባልደረባ ሜሮን አሐዱም ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የምታደርገዉ ግፊት ለአካባቢዉ መረጋጋት ጠንቅ ነዉ ይላሉ።ጋጤኛ አብረሃ በላይ ግን የዩናይትድ ስቴትስን ርምጃ «ተገቢ»፣ እንዲያዉም «የዘገየ» ብሎታል።

ታሪኩ ኃይሉ 

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ