1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዩናይትድ ስቴት ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ

ረቡዕ፣ ጥቅምት 25 2013

ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዲዴሞክራቶቹ  ተፎካካሪያቸው ጆ ባይደን በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ እጅግ የተቀራረበ ድምፅ ማግኘታቸው እየተዘገበ ነው።

https://p.dw.com/p/3ksTg
USA Wahlen 2020 | Donald Trump und Joe Biden
ምስል Jim Watson/AFP

ዶናልድ ትራምፕ ከወዲሁ ማሸነፋቸውን ይፋ አድርገዋል

ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እና የዲዴሞክራቶቹ  ተፎካካሪያቸው ጆ ባይደን በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንታዊ ምርጫ እጅግ የተቀራረበ ድምፅ ማግኘታቸው እየተዘገበ ነው። ጆ ባይደን በ50,1 ከመቶ እየመሩ ሲኾን፤ ዶናልድ ትራምፕ ስርጭታችን ከመጀመሩ አንድ ሰአት እስኪቀረው ድረስ 48,3 ድምጽ አግኝተዋል።  ይኽ በእንዲህ እንዳለ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከወዲሁ በምርጫው አሸናፊ መኾናቸውን ይፋ አድርገዋል። በአንዳንድ አካባቢዎች ደጋፊዎች ግጭት ውስጥ የገቡ ሲኾን፤ ፕሬዚደንቱ ይፋዊ መግለጫ ሳይሰጥ አሸነፍኩ ማለታቸው በዩናይትድ ስቴትስ ዴሞክራሲ ላይ ብርቱ ተግዳሮት መደቀኑን ተንታኞች ይናገራሉ። ምርጫውን በተመለከተ የዋሽንግተኑ ወኪላችን አበበ ፈለቀን ስቱዲዮ ከመግባታችን አስቀድሞ ቃለ መጠይቅ አድርጌለት ነበር። ምርጫውን እና የአሸነፍኩ አዋጁን ተከትሎ በዩናይትድ ስቴትስ ነዋሪዎች መካከል ስለተፈጠረው ስሜት በመግለጥ ይንደረደራል። 

አበበ ፈለቀ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
እሸቴ በቀለ