1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የየመን ጦርነት፣ ምክንያትና ዉጤቱ

ሰኞ፣ መጋቢት 20 2013

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዳስታወቀዉ  ከ230 ሺሕ ህዝብ በላይ ፈጅቷ፤ 4 ሚሊዮን አፈናቅሏል።22 ሚሊዮን ለረሐብና በሽታ አጋልጧል

https://p.dw.com/p/3rLnH
Yesuf Yassien
ምስል privat

ቃለ መጠየቅ፣ የየመን ጦርነትና ዉጤቱ

ሳዑዲ አረቢያ የምትመራዉ የአረብና የአፍሪቃ ተባባሪ ሐገራት ጦር የመንን ከወረረ ባለፈዉ ሳምንት አርብ 6ኛ ዓመቱን ደፍኗል።የሳዑዲ አረቢያ ገዚዎች ያኔ በ6 ሳምንታት ይጠናቀቃል ያሉት ጦርነት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዳስታወቀዉ  ከ230 ሺሕ ህዝብ በላይ ፈጅቷ፤ 4 ሚሊዮን አፈናቅሏል።22 ሚሊዮን ለረሐብና በሽታ አጋልጧል።ጦርነቱ አሁንም እንደቀጠለ ነዉ።የሳዑዲ አረቢያ ገዢዎች ግን ጦርነቱን በድርድር ለመፍታት እንደሚፈልጉ ባለፈዉ ሳምንት አስታዉቀዋል።የጦርነቱን ምክንያት፣ መዘዙንና የሰላም ጥሪዉን አስመልክተን ከፖለቲካ ተንታኝ ዩሱፍ ያሲን ጋር  ቃለ መጠይቅ አድርገናል።ሙሉዉን ቃለ መጠይቅ ከዚሕ ያድምጡ

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሰ