Tesfalem Waldyes Eragoሰኞ፣ ጥቅምት 24 2012በዕለቱ የዜና መጽሄት ሶስት ዘገባዎችን አካትተናል። በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ በመከላከያ ሰራዊት እና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ታጣቂዎች መካከል ውጊያ መቀስቀሱን የዓይን እማኞች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። የአዲስ አበባው ወኪላችን መግለጫውን ተከታትሏል። በኢትዮጵያ እየተከሰቱ ያሉ ግጭቶች ሀገሪቱ በምግብ ራስን ለመቻል ባስቀመጠችው ውጥን ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ የብሔራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።