1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዘንድሮው ምርጫ በኦሮምያ ክልል

ረቡዕ፣ መጋቢት 22 2013

ከምርጫው መገለላቸውን የሚገልጹት  የፖለቲካ ድርጅቶች የፖለቲካ አውድ መጥበብን በዋና ምክንያትነት ሲያቀርቡ መንግሥት በበኩሉ በኢትዮጵያ ከምን ጊዜውም በላቀ አመቺ የፖለቲካ አውድ አለ ሲል ይሞግታል፡፡

https://p.dw.com/p/3rS1a
Ethiopia, Addis Abeba | Oromia PP reaction on OFC withdrawal from the coming election
ምስል Seyoum Getu/DW

የዘንድሮው ምርጫ በኦሮምያ ክልል

 
በኦሮሚያ ክልል በስድስተኛ ብሔራዊ ምርጫ ተቀናቃኝ የፖለቲካ ድርጅቶች እንደተጠበቀው የነቃ ተሳትፎ አለማድረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ሊኖረው እንደሚችል ተገለፀ። በተለይም ከምርጫው በኋላ የሚገነባውን መንግሥታዊ እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ተቀባይነት በማጠናከር ዘላቂ ሰላም ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት እንዳይፈትን ያሰጋል ይላሉ አስተያየታቸውን ለዶቼቬለ የሰጡ አንድ የሕግ ባለሙያ፡፡ ከምርጫው መገለላቸውን የሚገልጹት  የፖለቲካ ድርጅቶች የፖለቲካ አውድ መጥበብን በዋና ምክንያትነት ሲያቀርቡ መንግሥት በበኩሉ በኢትዮጵያ ከምን ጊዜውም በላቀ አመቺ የፖለቲካ አውድ አለ ሲል ይሞግታል።

ስዩም ጌቱ

ኂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ