1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 የዓይደር ትምሕርት ቤት ድብደባ 22ኛ ዓመት

ዓርብ፣ ግንቦት 28 2012

ያም ሆኖ የዚያን ቀን መቀሌ ላይ የሆነዉ ይሆናል ብሎ የጠረጠሩ ከነበሩ እሱ  አንድም የአስመራን አዲስ ገዢዎችን ሚንስጥርና አስተሳሰብ በቅርብ የሚያዉቅ አለያም ነብይ መሆን አለበት።

https://p.dw.com/p/3dJsh
Äthiopien Mekelle | Schule | The Ayder
ምስል DW/M. Haileselassie

የዓይደር ትምሕር ቤት ድብደባ 22ኛ ዓመት

ኢትዮጵያና ኤርትራ የአንድ ሐገር አንድነታቸዉን አቋርጠዉ እንደ ሁለት ሐገራት መኖር ከጀመሩ ያኔ ገና 7 ዓመታቸዉ ነበር።የአዲስ አበባና የአስመራ አብያተ-መንግሥታትን የተቆጣጠሩት የቀድሞዎቹ አማፂያን ጥብቅ ፍቅር ግን ባድመ ላይ በተፈረጠዉ ጠብ መጎሽ ከጀመረ ወራት ተቆጠሩ።ያም ሆኖ የዚያን ቀን መቀሌ ላይ የሆነዉ ይሆናል ብሎ የጠረጠሩ ከነበሩ እሱ  አንድም የአስመራን አዲስ ገዢዎችን ሚንስጥርና አስተሳሰብ በቅርብ የሚያዉቅ አለያም ነብይ መሆን አለበት።ብዙዎቻችን ግን ብዙ ነገር እናዉቅ ነበር።ለምሳሌ ቀኑን።ልክ እንደ ዛሬዉ ሁሉ አርብ ነበር።ዕለቱም ግንቦት 28።ዓመቱ ግን 22 ዓመታት ወደ ኋላ ይተረተራል።1990።የመቀሌ ፀኃይ ጠንከር፣አየሯ ሞቅ ወበቅ ማለት ሲጀምር የዚያች  ከዓመታት ጦርነት በቅጡ ያላገገመችዉ ጥታዊ ከተማ ሰማይ አስገመገመ።ዓይደር ትምሕርት ቤት ----ያዩ ያስታዉሳሉ።

Äthiopien Mekelle | Schule | The Ayder
ምስል DW/M. Haileselassie

 ሚሊዮን ኃይለስላሴ

ነጋሽ መሐመድ

እሸቴ በቀለ