1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የዒድ አከባበር በሰበታ ከተማ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 24 2014

ሰሞኑን በኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች ተስፋፍቶ የተስተዋለው የሃይማኖት ግጭትን እንደሚያወግዙት የእምነቱ ተከታዮች እና የሃማኖቱ መሪዎች ገለጹ፡፡ ዛሬ በመላው ዓለም ተከብሮ የዋለው የኢድ አልፈጥር በዓል በኦሮሚያም በተለያዩ አከባቢዎች ተከብሯል፡፡

https://p.dw.com/p/4AjMy
Äthiopien Muslime in der Stadt Sebeta in der Region Oromia feiern Eid al-Fitr
ምስል Seyoum Getu/DW

የኢድ አልፈጥር በዓል ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ ተጠናቆአል

መሃመድ ኑር ሀሰን በኦሮሚያ ክልል የፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ሰበታ ከተማ ነዋሪ ነው፡፡ አቶ መሃመድን አግኝቼ ያነጋገርኳቸው ዛሬ በመላው ዓለም በድምቀት ተከብሮ የዋለውን የ1443ኛው ዓመተ ሂጂራ በሰበታ ከተማ ፉሪ አካባቢ ሲያከብሩ ነው፡፡  በወርሃ ረመዳን አቅማቸው የፈቀደላቸው የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ በሙሉ ስርዓተ ጾሙን ያከናውናሉ፡፡ አቅማቸው ያልፈቀደላቸው አረጋውያን እና ህሙማንም ቢሆን ባይጾሙ እንኳ ሃይማኖቱ በሚደነግገው መልኩ መክፈል ያለባቸውን ከፍለው በዚህች የኢድ አልፈጥር ቀን ተካፋይ ይሆናሉ፡፡ የፉሪ 25 መስጊዶች እና የኢድ ሰብሳቢ ሲራጅ ፈድሉ ያሲን እለቱን አስመልክተው አስተያየታቸው ያጋሩን የሃማኖቱ መሪ ናቸው፡፡ እንደ የሃይሞኖት መሪው ማብራሪያ ይህቺ የረመዳን ወር ፍጻሜ የኢድ ቀን ልዩ ትርጉምና ስፍራ እንዳላትም አብራርተውልናል፡፡  የእምነት አባቶቹ እና የሃይማኖቱ ተከታዮች በአስተያየታቸው አክለውም በቅርቡ በኢትዮጵያ እያገረሸ የመጣው የሃሞኖት ግጭት አገርንም ሆነ ሃማኖቶቹን ሚጎዳ በመሆኑ በስክነት ሊያዝ የሚገባው ነው ብለዋል፡፡ ዛሬ ከማለዳው 12 ሰአት ጀምሮ በርካታ ሕዝበ ሙስሊም ወደ አደባባይ በወጡበት በዚህ ሰበታ ከተማ የተከበረው የኢድ አልፈጥር በዓል ፍጹም ሰላማዊ ሆኖ ነው የተጠናቀቀው፡፡ ሁሉም ሙስሊም ቅዱሱን የረመዳን ወር በፆም አሳልፈው በህብረት ሶላት በማድረስ የሚያከብሩት በዓሉ በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም ተከብሮ ውሏል።

ስዩም ጌቱ 

አዜብ ታደሰ 

እሸቴ በቀለ