1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

«የፀጥታ ኃይሉ ተመጣጣኝ እርምጃ አለመውሰዱን የሚያመላክቱ ነገሮች አሉ»ኢሰመኮ

ረቡዕ፣ ነሐሴ 6 2012

ኮሚሽኑ እንዳለው ጉዳዩን በስፍራው ተገኝቶ ለማጣራትና ለመገምገም መርማሪ ቡድን ለመላክ ዝግጅቱን አጠናቋል።ሆኖም  ወደ አካባቢው የሚወስደው መንገድ መዘጋቱ እንቅፋት እንደሆነበት ገልጿል። የኮሚሽኑ የሃዋሳ ቅርንጫፍ አስተባባሪ  በዞኑ የተለያዩ ከተሞች በተከሰቱ ግጭቶች «የፀጥታ ኃይሉ ተመጣጣኝ እርምጃ አለመውሰዱን የሚያመላክቱ ነገሮች አሉ ብለዋል።

https://p.dw.com/p/3gr2C
Äthiopien Proteste Wolita Zone
ምስል Addis Standerd

«የፀጥታ ኃይሉ ተመጣጣኝ እርምጃ አለመውሰዱን የሚያመላክቱ ነገሮች አሉ»ኢሰመኮ

  

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በደቡብ ክልል በወላይታ ዞን በቁጥጥር ሥር የዋሉ የዞኑ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እስከ ትናንት ድረስ ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ አስታወቀ።ኮሚሽኑ እንዳለው ጉዳዩን በስፍራው ተገኝቶ ለማጣራት እና ለመገምገም መርማሪ ቡድን ለመላክ ዝግጅቱን አጠናቋል።ሆኖም  ወደ አካባቢው የሚወስደው መንገድ መዘጋቱ እንቅፋት እንደሆነበት ገልጿል።በሌላ በኩል ዶቼቬለ ያነጋገራቸው የኮሚሽኑ የሃዋሳ ቅርንጫፍ አስተባባሪ  በዞኑ የተለያዩ ከተሞች ነሐሴ 4፣2012 ዓም በተከሰቱ ግጭቶች «የፀጥታ ኃይሉ ተመጣጣኝ እርምጃ አለመውሰዱን የሚያመላክቱ ነገሮች አሉ ብለዋል።ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝሩን ያቀርብልናል።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
አዜብ ታደሰ