1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የውጭ ጉዳይ ሚንሥቴር መግለጫ

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 26 2013

የአውሮጳ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንደማይልክ ያሳወቀው ሕብረቱ ያቀረበውን በቅኝ ተገዢ ሀገር እና መንግሥት ካልሆነ በቀር በነፃ ሀገር ሊፈቀድ የማይችል ቅድመ ሁኔታ ኢትዮጵያ ባለመቀበሏ መሆኑ ተገለ።

https://p.dw.com/p/3sxU4
Äthiopien Ambassador Dina Mufti
ምስል Solomon Muchie/DW

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚፃረር ነው

የአውሮጳ ሕብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን እንደማይልክ ያሳወቀው ሕብረቱ ያቀረበውን በቅኝ ተገዢ ሀገር እና መንግሥት ካልሆነ በቀር በነፃ ሀገር ሊፈቀድ የማይችል ቅድመ ሁኔታ ኢትዮጵያ ባለመቀበሏ መሆኑ ተገለ። በሕብረቱ የቀረቡት ቅድመ ሁኔታዎች የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚፃረሩ፣ ነፃነቷን የሚዳፈሩ እና ደህነቷን አደጋ ላይ የሚጥሉ መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። የሱዳንን ወቅታዊ አቋም «ቅጥ ያጣ ድፍረት» ያለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ እስካሁን ያሳየችው ትዕግስት ለመልካም ጉርብትና፣ ለሰላም እና ለቀጣናው ካላት ክብር የመነጨ ነው ብሏል። ሆኖም የሱዳን መንግሥት ኢትዮጵያን በሚመለከት የሚያወጣው መግለጫ ከሰሞኑ የቤኒሻንጉል መሬት የእኔ ነው እስከሚል መለጠጡን አውግዟል። 

ሰለሞን ሙጬ
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አዜብ ታደሰ