1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋዜጣዊ መግለጫ 

ሐሙስ፣ ጥቅምት 11 2014

በሕገ ወጥ መንገድ በጠብመንጃ ችግር እፈታለሁ ከሚለው ኃይል ውጪ ካሉት ጋር ባዘጋጀው የሰላም ፍኖተ ካርታ ላይ ለመነጋገር በዝግጅት ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ መንግሥት አስታውቋል። (ሕወሓት) መቀሌ ውስጥ ለጦር መሣሪያ መጋዘን፣ ጥገና እና መስሪያ የሚጠቀምባቸው ቦታዎች ላይ የተፈፀመው የአየር ድብደባ ንፁሃንን ዒላማ አላደረገም ብሏል መንግሥት።

https://p.dw.com/p/41zpR
Äthiopien l Sprecher des Außenministeriums - Dina Mufti
ምስል Solomon Muchie/DW

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋዜጣዊ መግለጫ 

መንግሥት በሕገ ወጥ መንገድ በጠብመንጃ ችግር እፈታለሁ ከሚለው ኃይል ውጪ ካሉት ጋር ባዘጋጀው የሰላም ፍኖተ ካርታ ላይ ለመነጋገር በዝግጅት ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። ይህ የተገለጸው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው። ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) መቀሌ ከተማ ውስጥ ለጦር መሣሪያ መጋዘን፣ ጥገና እና መስሪያ የሚጠቀምባቸው ቦታዎች ላይ የተፈፀመው የአየር ድብደባ ንፁሃንን ዒላማ እንዳላደረገም በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተጠቅሷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል ዐቀባይ በሌሎች ጉዳዮች ላይም ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል። 

ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ነጋሽ መሐመድ