1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 13 2013

በዛሬው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሳምንታዊ መግለጫ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቱርክ ጉብኝትና የሁለቱ ሃገራት ስምምነቶች፤ የአሜሪካ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ መልዕክተኛ የኢትዮጵያን ቆይታ፤ ከሳውድ አረቢያ ስለሚመለሱ ዜጎች ጉዳይ፤ ስለሚዘጉ ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች ማብራሪያ ተሰጥቷል።

https://p.dw.com/p/3zBCR
Äthiopien Logo des Außenministeriums

የውጭ ጉዳይ ሳምንታዊ መግለጫ

 

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ታይፕ ኤርዶጋን ጋር በውኃ ልማትና መከላከያ ዘርፎች ላይ ስምምነት መፈራረማቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። ቱርክ በኢትዮጵያ ውስጥ ከቻይና ቀጥላ ሰፊ የንግድና የመዋዕለ ነዋይ ፍሰት ተሳትፎ ያላት አገር በመሆኗ ጉብኝቱ ይህንንም ይበልጥ ለማሳደግ እንደሚያግዝም አመልክቷ። በዛሬው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ሳምንታዊ መግለጫ የአሜሪካ የምሥራቅ አፍሪካ ልዩ መልዕክተኛ የኢትዮጵያን ቆይታ፤ ከሳውድ አረቢያ ስለሚመለሱ ዜጎች ጉዳይ፤ ስለሚዘጉ ቆንስላ ጽሕፈት ቤቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ሰሎሞን ሙጬ 

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ