1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የውጭ ንግድ የገጠመው ችግር

ሰኞ፣ ጥቅምት 10 2012

በኢትዮጵያ የውጭ ንግድ በስርአት ባለመመራቱ ውድድርን እያቀጨጨ መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።  በውጭ ንግዱ ውስጥም የሀገር ስም የሚያገድፉ ያላቸውን ተአማኒነት የጎደለው  የንግድ ባህሪ  ያሳዩትን የንግድ ፈቃዳቸውን ለጊዜው እያገደ መሆኑንም አመለከተ። 

https://p.dw.com/p/3RfOR
Misganu Arega
ምስል DW/S. Muchie

«በሥርዓት አለመመራቱ ውድድሩ ላይ ችግር አስከትሏል»

 ዶላርን በመፈለግ ሰበብ በውጭ ንግድ ውስጥ መግባት፣ የሀገር ውስጥ ምርቶችን ዋጋ ከዓለም አቀፍ ዋጋ እጅግ አሳንሶ መላክ፣ የኮንትራት ክህደት መፈጸምና የውጭ ምርቶችን ደብቆ ለሀገር ውስጥ ገበያ ማቅረብ፤ ዋና ችግሮች መሆናቸውን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምሥጋኑ አረጋ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አመልክተዋል።
ይህም በመሆኑ ከተለያዩ ሃገራት በኢትዮጵያዊ ላኪዎች የውል ክህደት ተፈጸመብን የሚሉ ተደጋጋሚ ቅሬታዎች የንግድ አጋሮች ለኢትዮጵያ መንግሥት እንደመጣም ተናግረዋል።  ይህንን የዘርፉን ሥራ እንዲያሽቆለቁል ያደረገውን ችግር ለመፍታት ላኪዎች በውል መሠረት፣ በተጠያቂነትና በፍትሃዊነት ሥራቸውን እንዲያከናውኑ የሚያስገድድ አዲስ የኮንትራት አስተዳደር ሥርአት መዘርጋቱንም አብራርተዋል። ከአዲስ አበባ ዝርዝር ዘገባ ደርሶናል።

ሰለሞን ሙጬ

ሸዋዬ ለገሠ

ተስፋለም ወልደየስ