የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ጋዜጣዊ መግለጫ
ዓርብ፣ ሐምሌ 27 2010ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ የመሩት የመልዕክተኞች ቡድን ዩናያትድ ስቴትስ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ጋር ከተነጋገረ ወዲሕ ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባዉ እና ለመግባት የሚጠይቀዉ ኢትዮጵያዊ ቁጥር መጨመሩን የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር አስታወቀ። የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም ዛሬ ለጋዜጠኞች እንደነገሩት የጠቅላይ ሚንስትሩ ጉብኝት ከፍተኛ ዉጤት አስገኝቷል። አቶ መለስ በዛሬዉ መግለጫቸዉ ኢትዮጵያ፤ ኤርትራ እና ጅቡቲን ለማስታቀር እንደምትሸመግልም አስታዉቀዋል። ኢትዮጵያ፤ ሁለቱን ሐገራት ለማስታረቅ፤ ቃል አቀባዩ እንዳሉት፤ በኃላፊነት ስሜት ትጥራለች። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ጌታቸዉ ተድላ ኃይለ ጊዮርጊስ
ነጋሽ መሐመድ
ሸዋዬ ለገሰ