1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኮቪድ 19 ክትባት በብሪታንያ

ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 1 2013

የተለያዩ ሃገራት የመድኃኒት አምራች ኩባንያዎች መከላከያ ክትባት እየቀመምን ነው ቢሉም በምዕራቡ ዓለም ተቀባይነት ያገኘው ፋይዘርና ባዮንቴክ የተባሉት ኩባንያዎች የደረሱበት ግኝት ነው።

https://p.dw.com/p/3mXPh
Coronavirus | Impfstoff
ምስል Robin Utrecht/picture alliance

«ብዙዎች መከተብ ይፈልጋሉ»

ብሪታንያ ከትናንት በስተያ ማክሰኞ አንስቶ የኮቪድ 19 ክትባትን ለዜጎቿ መስጠት ጀምራለች። ላለፉት 10 ወራት በተለይ በአውሮጳና በቀረው የዓለም ክፍል ከፍተኛ ስጋትና ሌላው ቀርቶ የመንቀሳቀስ ነፃነት ላይ ሳይቀር ጫና ያሳደረው የኮሮና ወረርሽኝ የተመራማሪዎችን አቅምና ዕውቀት ፈተና ውስጥ ከቷል። የተለያዩ ሃገራት የመድኃኒት አምራች ኩባንያዎች መከላከያ ክትባት እየቀመምን ነው ቢሉም በምዕራቡ ዓለም ተቀባይነት ያገኘው ፋይዘርና ባዮንቴክ የተባሉት ኩባንያዎች የደረሱበት ግኝት ነው። ለዚህ ምርምር ውጤት እውቅና የሰጠችው ብሪታንያ ክትቧቱን ለአዛውንት በመስጠት ብትጀምርም የጉሮሮ ህመምና የመተንፈስ ችግር ያስከተለባቸው እንዲሁም የሰውነት መቆጣት ያጋጠማቸው አሉ ተብሏል። ይህ በኅብረተሰቡ የመከተብ ፍላጎት ላይ ያሳደረው ነገር ይኖር ይሆን? 

ድልነሳ ጌታነህን

ሸዋዬ ለገሠ

አዜብ ታደሰ