የኮሎኙ የናዚ ጀርመን ሚስጥራዊ ማጎሪያ ጣቢያ
ማክሰኞ፣ ታኅሣሥ 12 2003ማስታወቂያ
እስከዛሬ ድረስ በባለቤቱ በሊዮፖልድ ዳህማን ስም ነው የሚጠራው ። እ.ጎ.አ በ 1935 ነበር ፣ በግንባታ ላይ የነበረውን ይህን ህንፃ ናዚዎች ወርሰው የሚስጥራዊ የፖሊስ ኃይል በጀርመንኛው ምህፃር ጌስታፖ ዋና ፅህፈት ቤት ያደረጉት ። ህንፃው አሁን በናዚ በግፍ የተገደሉ እና ብዙ መከራ እና ስቃይ የደረሰባቸው ሰዎች መታሰቢያ ስፍራ ነው ። በየቀኑ በርካታ ጎብኝዎችን በሚያስተናግደው በዚህ ህንፃ « በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የሶስተኛው ዓለም ሚና የተሰኘ አውደ ርዕይ በመታየት ላይ ነው ። በአውሮፓውያን ታሪክ ዕምብዛም የማይታወቀውን በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የሶስተኛው ዓለም ህዝቦችን ሚና ባለፈው ሳምንት ዝግጅታችን አንስተን ቀሪውን ዛሬ ልናጠናቅቅ አውደ ርዕዩ የቀረበበትን ህንፃ ታሪክም ልናስቃኝ ቃል በገባነው መሠረት በሰዓታችን ቀርበናል ።
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሰ