የእሳት ቃጠሎ በአዲስ አበባ
ረቡዕ፣ ነሐሴ 27 2012ማስታወቂያ
ዛሬ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስምንት ሲኤምሲ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ የእሳት ቃጠሎ አደጋ በርካታ የሕንጻ መሣሪያ መሸጫ ሱቆች ከባድ ጉዳት ደረሰባቸው። በተለይም ገስት ሦላር በተባለው ሕንጻ ስር የሚገኙ የተለያዩ መደብሮች በእሳት ጋይተዋል። የእሳት አደጋውን ለመከላከል 14 ተሽከርካሪዎች የተሰማሩ ሲሆን እሳቱን ለማጥፋት ከ 4 ሰዓታት በላይ ወስዷል። አምስት የእሳት አደጋ ተከላካይ ሠራተኞች መጠነኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ አደጋ የለም። መንግሥት የደረሰውን ጉዳት በዝርዝር እያጣራሁ ነው ብሏል። አንድ ሱቃቸው የተቃጠለባቸው ነጋዴ ከ30 በላይ ሱቆችና ተጨማሪ መጋዝኖች ሳይወድሙ እንዳልቀረ ተናግረዋል። ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ተጨማሪ ዘገባ አለው።
ሰሎሞን ሙጬ
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋኅ መሐመድ