1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢድ አል አድሃ በሳዑዲ

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 15 2010

ሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንም በዓሉን በመንፈሳዊ ሥርዓት አክበረዉ ዉለዋል። ለሐጅ ሥርዓት እዚያዉ ሳዑዲ አረቢያ የሚገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ጉባኤ ፕሬዝደንት ሐጂ መሐመድ አሚን ጀማል ለመላዉ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

https://p.dw.com/p/33WKh
Saudi-Arabien Hadsch-Wallfahrt in Mekka
ምስል picture-alliance/dpa/CIC

የኢድ አል አድሐ በዓል በሳዑዲ አረብያ

ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ የኢድ አል-አድሃ በዓል ዛሬ በይፋ የተጀመረዉ መካ ዉስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሑጃጆች ባደረጉት የስግደት ፀሎት ነዉ። በፀሎቱ ላይ የሳዑዲ አረቢያዉ ንጉስ እና የሐገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ተገኝተዋል። እዚያዉ ሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንም በዓሉን በመንፈሳዊ ሥርዓት አክበረዉ ዉለዋል። ለሐጅ ሥርዓት እዚያዉ ሳዑዲ አረቢያ የሚገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ጉባኤ ፕሬዝደንት ሐጂ መሐመድ አሚን ጀማል ለመላዉ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የጂዳዉ ወኪላችን ነብዩ ሲራክ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ነብዩ ሲራክ

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ