የኢዜማ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ከወጣቶች ጋር ተወያዩ
እሑድ፣ ነሐሴ 26 2011ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ዛሬ በአዲስ አበባ መዘጋጃ ቤት አዳራሽ ከወጣቶች ጋር ተወያይተዋል። በዚህም ውይይት ላይ ወጣቶች ለሀገራቸው ከፍተኛ ሚና ሊያበረክቱ እንደሚችሉ ተገልጿል። የኢዜማ ወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ ወይዘሪት ፂዎን እንግዳዬ « ሀገራችንን ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ማሸጋገር እንችላለን» ብለዋል።ይህንኑ ስብሰባ የተከታተለው የአዲስ አበባው ወኪላችን ዮሀንስ ገብረ እግዚያንሔር ዘገባ እንዲህ አይነት የውይይት መድረክ መዘጋጀቱን ታዳሚያን ማወደሳቸውን ይገልፃል።
ዮሀንስ ገብረ እግዚያንሔር
ልደት አበበ