1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የድጋፍ እና የተቃውሞ ሰልፍ በፓሪስ

ቅዳሜ፣ ሰኔ 29 2011

የተቃውሞው ሰልፍ አስተባባሪዎች እንዳሉት የሰልፉ ዓላማ የኢትዮጵያ ስርዓት በአማራ ላይ ያደርሳል የሚሉትን በደል ማሳወቅ ነው።ሌላኛ ሰልፍ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሚመሩትን ለውጥ በመደገፍ የተካሄደ  ሲሆን የሰልፉ ተካፋዮች የዐቢይን ስም ለማጥፋት መጡ ላሏቸው ተቃዋሚዎች ዐብይ ጥፋተኛ እንዳልሆኑ ለማመልከት መሰለፋቸውን ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/3LhJP
Frankreich Äthiopier demonstrieren in Paris
ምስል DW/H. Tiruneh

የፓሪሱ የኢትዮጵያውያን የድጋፍ እና የተቃውሞ ሰልፍ

 
ዛሬ ፓሪስ ፈረንሳይ ውስጥ ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያን መንግሥት የሚቃወሙ እና የሚደግፉ ሰልፎች በተመሳሳይ  ቦታ በተመሳሳይ ሰዓት አካሂደዋል። የተቃውሞውን ሰልፍ ያስተባበረው በፈረንሳይ የአማራ ማህበር ነው።አስተባባሪዎቹ የሰልፉ ዓላማ በኢትዮጵያ ስርዓቱ በአማራ ላይ ያደርሳል የሚሉትን በደል ለማሳወቅ መሆኑን ለዶቼቬለ ተናግረዋል።ሌላኛ ሰልፍ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሚመሩትን ከዛሬ አንድ ዓመት ወዲህ የሚካሄደውን ለውጥ እና የመንግሥታቸውን እርምጃ በመደገፍ የተካሄደ ነበር። የዚሁ ሰልፍ ተካፋዮች ፣የዶክተር አቢይን ስም ለማጥፋት መጡ ላሏቸው ተቃዋሚዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥፋተኛ እንዳልሆኑ እና ለሁሉም ዜጎች እንደሚሰሩ ለማመልከት መሰለፋቸውን ተናግረዋል።በስፍራው የተገኘችው የፓሪስዋ ዘጋቢያችን ሃይማኖት ጥረነህ  ቀጣዩን ዘገባ አጠናቅራለች።
ኃይማኖት ጥሩነህ 
ኂሩት መለሰ

Frankreich Äthiopier demonstrieren in Paris
ምስል DW/H. Tiruneh