1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

 የኢትዮጵያና የግብፅ ልዩነት 

ሐሙስ፣ መስከረም 8 2012

የኢትዮጵያ፣የሱዳንና የግብፅ የዉኃ ሚንስትሮች ባለፈዉ ዕሁድና ሰኞ ካይሮ ዉስጥ ባደረጉት ስብሰባም መፍትሔ ላይ ሳይደርሱ በቀጠሮ ተለያይተዋል

https://p.dw.com/p/3PtjO
Grand Ethiopian Renaissance Dam
ምስል picture-alliance/dpa/G. Forster

የኢትዮ-ግብፅ ልዩነት በፖለቲካ ተንታኙ እይታ

ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ በምታስገነባዉ ግዙፍ የኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ ሰበብ ከግብፅ ጋር የገጠመችዉ አለመግባባት እስካሁን ሁነኛ መፍትሔ አላገኘም።የኢትዮጵያ፣የሱዳንና የግብፅ የዉኃ ሚንስትሮች ባለፈዉ ዕሁድና ሰኞ ካይሮ ዉስጥ ባደረጉት ስብሰባም መፍትሔ ላይ ሳይደርሱ በቀጠሮ ተለያይተዋል።የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ሶስቱ ሐገራት በየፊናቸዉ የገጠማቸዉ ፖለቲካዊ ቀዉስ እስካሁን ለዘለቀዉ አለመግባባት ሌላ መልክና ባሕሪ እየሰጠዉ ነዉ።በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የዉጪ ግንኙነት መምሕር አቶ የማነ ዘርዓት እንደሚሉት ደግሞ ግብፅ የኢትዮጵያና የሱዳን ወቅታዊን በመጠቀም ፍላጎቷን ለማስፈፀም እየጣረች ይመስላል።

ሚሊዮን ኃይለ ስላሴ 

ነጋሽ መሐመድ

ኂሩት መለሰ