አነጋጋሪው የኢትዮጵያና ሱዳን ግንኙነት
ሰኞ፣ ነሐሴ 3 2013ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ ይዞታዬ ነው የምትለውን መሬት በኃይል የያዘችው ሱዳን የኢትዮጵያ መንግሥትን በሽብርተኝነት ከተፈረጀው ህወሓት ጋር ለማደራደር ያወጣችው እቅድ በጎ ምላሽ ሳያገኝ ከቀረ በኋላ አምባሳደሯን ከኢትዮጵያ ጠርታለች። ማደራደር የተባለውን ሃሳብም የጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት ሱዳን በወቅታዊ አቋሟ እምነት የሚጣልባት እንዳልሆነች በመጥቀስ ውድቅ አድርጎታል።አሜሪካ ለረጅም ዘመን ጫና ውስጥ አስገብታት ከነበረችው ሱዳን ጋር አሁን አዲስ ግንኙነት ስትመሰርት ለረጅም ጊዜ ወዳጇ ለኢትዮጵያ ጀርባዋን ሰጥታለች።ኢትዮጵያ በበኩሏ ድንበሯ በኃይል ተይዞ ችግሩ አሁንም በሰላም እንዲፈታ ሱዳንም ከያዘችው የኢትዮጵያ መሬት ለቅቃ እንድትወጣ እየጠየቀች ነው።ለመሆኑ ረጅም ድንበር የሚጋሩት የኢትዮጵያና ሱዳን የሁለትዮሽ ግንኙነት ወዴት እያመራ ይሆን ? ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዘገባ አለው።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ