የኢትዮጵያ ጦርነትና ብሔራዊ ዉይይት
ሐሙስ፣ ነሐሴ 27 2013ማስታወቂያ
ኢትዮጵያ መንግሥት «ሁሉንም አሳታፊ» ያለዉን ሐገር አቀፍ ዉይይት ለማድረግ በመጪዉ የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ጉባኤ ጠርቷል።ይሁንና የገዢዉ ፓርቲ ባለስልጣናት እንደሚሉት በዉይይቱ በጠመጃ የሚዋጉ ኃይላት አይጋበዙም።ኢጋድ፣ የአፍሪቃ ሕብረትና ሌሎች የዉጪ ወገኖች 10 ወራት ያስቆጠረዉን ጦርነት በድርድር ለመምፍታት ያቀረቡት ሐሳብም እስካሁን ተቀባይነት ያገኘ አይመስልም።ተፋላሚ ኃይላት አንዳቸዉ ሌላቸዉን መዉቀስና ማዉገዛቸዉም እንደቀጠለ ነዉ።ጦርነትና መወጋገዙ በቀጠለበት ባሁኑ ወቅት የተጠራዉ ሐገር አቀፍ ዉይይት ምን ዉጤት ያመጣ ይሆን?
ስዩም ጌቱ
ነጋሽ መሐመድ
ኂሩት መለሰ