1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ማስጠንቀቂያ

ረቡዕ፣ ግንቦት 11 2013

በዩትዩብ መረጃ የሚያሰራጩ ተቋማት እና ግለሰቦች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ እንዲመዘገቡ የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አሳሰበ። ባለስልጣኑ ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ9 ወራት የስራ አፈጻጸሙን ባስገመገመበት ወቅት እንዳለው በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው በማይሰሩ ተቋማትም ሆነ ግለሰቦች ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል።

https://p.dw.com/p/3tblL
Äthiopien | Parlamentsdebatte zu Rolle der Medien
ምስል Yohannes Gebireegziabher/DW

በዩትዩብ መረጃ የሚያሰራጩ ተቋማት እና ግለሰቦች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ እንዲመዘገቡ

በዩትዩብ መረጃ የሚያሰራጩ ተቋማት እና ግለሰቦች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ እንዲመዘገቡ የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አሳሰበ። ባለስልጣኑ ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የ9 ወራት የስራ አፈጻጸሙን ባስገመገመበት ወቅት እንዳለው በህጋዊ መንገድ ተመዝግበው በማይሰሩ ተቋማትም ሆነ ግለሰቦች ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል። በምክር ቤቱ የሕግ ፍትህ እና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር በተደረገው ውይይት ባለስልጣኑ በፋይናንስ ኃብት አጠቃቀሙ ተገምግሟል።

ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር

ታምራት ዲንሳ

ነጋሽ መሐመድ