1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ውይይት በአውሮጳ

ሰኞ፣ ሐምሌ 8 2011

የኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ግንባታ ፕሮጀክት የአውሮፓ ኮንፍረንስ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ፤ ከሐምሌ 5 ጀምሮ፤ ለሁለት ቀናት በኔዘርላንዷ ደናህግ ከተማ ተካሂዷል። በስብሰባው ላይ በቅርቡ በኔዘርላንድስ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አቶ ሚሊዮን ሳሙኤል ተገኝተዋል።

https://p.dw.com/p/3M7Jj
Äthiopien - feiernde Menschen unter Staatsflagge
ምስል AP

የኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት ግንባታ ውይይት በአውሮፓ

ኢትዮጵያ ያልተቋረጠ የቀደመ የሀገረ መንግስት ታሪክ ያላት ብትሆንም እስካሁን ግን ፍጹም ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ መሆን አልቻለችም። በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ በአንድ በኩል ጥንታዊ የስነ ጽሁፍ እና የስነ ጥበብ ባለቤት፣ የነጻነት ተምሳሌት በመሆን በሌላ በኩል ደግሞ ድህነት የሰፈነባት፣ ግጭት እና ጦርነት የሚካሄድባት እና አምባገነናዊ አስተዳደር የሰፈነባት ሀገር በመሆን ታውቃ ቆይታለች።

የሀገረ ግንባታ ፕሮጀክት አጀማመርም ከዚህ መሰረታዊ አስተሳሰብ በመነሳት ኢትዮጵያውያን ያለፉትን ጥሩ እና ጥሩ ያልሆኑ ታሪኮቻቸውን ተቀብለው የአሁኗን እና የወደፊቷን ኢትዮጵያ በእኩልነት እና በመከባበር ላይ እንዲመሰርቱ  ለማገዝ እንደሆነ ተገልጿል። በደህናጉ ስብሰባ ላይ የስዊዲን፣ የኔዘርላንድስ እና የቤልጂየም የሀገር ግንባታ ታሪኮች እና ልምዶችም ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ከጀርመን፣ ቤልጄየም እና ከስካንዲኒቪያ ሀገራት የመጡ የልዩ ልዩ ስብስቦች ተወካዮች እና አባላት ስብሰባውን ተሳትፈዋል። 

የፕሮጀክቱን ዓላማ ለማሳካት በኢትዮጵያ ውስጥ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉባቸው ሲምፖዚየሞች እና ስብሰባዎች መካሄዳቸውን የፕሮጀክቱ ግብረ ኃይል ሰብሳቢ ፕሮፌሰር ካሳሁን ብርሃኑ ገልጸዋል። በአውሮፓ እና በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ለመሳተፍም ጥረት መደረጉን እና ውጤቶችም መገኘታቸውን ለዶይቼ ቬለ አብራርተዋል።  

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ የድምጽ ማዕቀፉን ይጫኑ። 

ገበያው ንጉሴ

ተስፋለም ወልደየስ

አዜብ ታደሰ