1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የኢትዮ ቴሌኮም የ3ዓመት ዕቅድ

ዓርብ፣ ነሐሴ 24 2011

ኢትዮ ቴሌኮም ተቋሙን ተወዳዳሪ፤ ብቁ እና ተመራጭ  ማድረግ  ያስችላል ያለውን የሦስት ዓመታት ስልታዊ  ዕቅዱን ዛሬ ይፋ አደረገ። ኢትዮ ቴሌኮም የነደፈው  ስልት  ከሐምሌ 2011  እስከ ሰኔ 2014ዓ,ም  የሚያገለግል መሆኑን ዛሬ አስታውቋል።

https://p.dw.com/p/3Olc1
Frehiwot Tamiru  Ethio Telecom
ምስል DW/ S.Muchie

«በተጀመረው የበጀት ዓመት የባለቤትነት ለውጥ አያመጣም»

 የተቋሙም  መዳረሻ  ያመላክታል የተባለው  ይህ ስልት በተያዘው  የመንግሥት የበጀት አመት በተቋሙ  ላይ  የባለቤትነት ለውጥ  እንደማያመጣ እና በመንግሥት ይዞታ ሥር እንደሚቆይም ተነግሯል።  ይሁንና በሚቀጥሉት  አመት  የተቋሙ የባለቤትነት ጉዳይ  ላይ ሌሎች አካላት እንዲሳተፉበት እንደሚደረግ  የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ ዛሬ በሰጡት መግለጫ አመልክተዋል። 

ኢትዮ ቴሌኮም  የዓመቱን  የቢዝነስ  ዕቅድ  ሲያስቀምጥም  የደንበኞቹን  ቁጥር  ከ43.6 ሚሊዮን  ወደ 50.4 ፣ የገቡ መጠኑንም በ2011 መጨረሻ  አሁን ካለበት 36.3 ቢሊዮን  ወደ 45.4 ቢሊዮን ለማሳደግ  ማቀዱን  አመልክቷል። ተቋሙ  እንዳለው  የደንበኞች  ፍላጎት  ከድምፅ  አገልግሎት ይልቅ የሞባይል ኢንተርኔት  አገልግሎት  ላይ እያደገ  በመምጣቱ የሚከናወኑ የማሻሻጻ ሥራዎች በዚሁ ላይ የሚያተኩር ይሆናል። የገቢ ምንጬንም አሁን ካሉ በላይ ሌሎች አገልግሎቶችን በማቅረብ ለማሳደግ መወጠኑንም አመልክቷል። ሰሎሞን ሙጬ ከአዲስ አበባ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።

ሰሎሞን ሙጬ

ሸዋዬ ለገሠ

ተስፋለም ወልደየስ