1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

  የአፋር ክልል ስሞታ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 20 2013

ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) በሚቆጣጠራቸዉ የአፋር ክልል ወረዳዎች የሚኖረዉን አርብቶ ደር ሕዝብ እየበደለ፣ ሐብትና ንብረትም እየዘረፈ ነዉ በማለት የአፋር ክልል መስተዳድር ወቀሰ።

https://p.dw.com/p/3y8wZ
Äthiopien Konflikte
ምስል Eduardo Soteras/AFP/Getty Images

  የአፋር ክልል ስሞታ

  
ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) በሚቆጣጠራቸዉ የአፋር ክልል ወረዳዎች የሚኖረዉን አርብቶ ደር ሕዝብ እየበደለ፣ ሐብትና ንብረትም እየዘረፈ ነዉ በማለት የአፋር ክልል መስተዳድር ወቀሰ። የክልሉ የኮሙኒኬሽን ፅሕፈት ቤት ኃላፊ አሕመድ ከሎይታ እንደሚሉት የሕወሓት ታጣቂዎች በተቆጣጠሯቸዉ አካባቢዎች ይኖር የነበረ 75ሺሕ ሕዝብ ከቤት ንብረቱ ተፈናቅሏል። ሕወሓት እስካለፈዉ ሳምንት ድረስ ከአፋር ክልል 4 ወረዳዎችን መቆጣጠሩን አቶ አሕመድ አረጋግጠዋል። በተያያዘ ዜና ሰሞኑን በአፋርና በሶማሌ ክልል አዋሳኝ ድንበር አካባቢ ተቀስቅሶ የነበረዉ ግጭት መቆሙን የአፋር  ባለስልጣናት አስታዉቀዋል።

ሰለሞን ሙጬ 

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ