1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዴፓ እና አዴኃን ውሕደት

ማክሰኞ፣ ኅዳር 4 2011

የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ ውህደት ፈጥረው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ) በሚል ስያሜ ለመጠራት ተስማሙ። የአማራ ክልል ገዥ ፓርቲ አዴፓ ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ምግባሩ ከበደ የፓርቲዎቹ ቅንጅት መፍጠር የህዝብ ጥያቄዎችን ለመመለስ እንደሚያስችልና ለሌሎች ፓርቲዎችም አረአያ ይሆናል ብለዋል፡፡

https://p.dw.com/p/38AVR
Fasil Schloss Gonder Äthiopien
ምስል DW/Azeb Tadesse Hahn

«ውህደታቸው ለአማራ ጥያቄ ምላሽ በጋራ ለማግኘት ይረዳል»

አዴፓ እና አዴኃን ወደአንድነት መምጣት መቻላቸው ጠንካራ አንድነት ለመፍጠር ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ያሉት አቶ ምግባሩ ውህደቱ የመድበለ ፓርቲን ያዳክማል የሚል እሳቤም እንደሌለው ተናግረዋል። የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ የታገለላቸው ሀሳቦች አዴፓም በአቋም እንደሚቀበላቸው አመልክተዋል፡፡

ስለሆነም ሁለቱ ድርጅቶች መዋሃዳቸው ለአንድ ዓላማ መቆማቸውን እንደሚያሳይ ያመለክታል ብለዋል፡፡ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ  ውህደት ፈጥረው የጋራ መጠሪያቸው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (አዴፓ)  እንዲሆን መወሰኑን አቶ ምግባሩ አስረድተዋል፡፡ ውህደት የፈጠረው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ የመረጃና ደህንነት ኃላፊ አቶ ፍፁም አየነው በበኩላቸው የአማራ ክልልን ህዝብ ጥያቄዎች ባግባቡ ለመመለስና ጠንካራ ክልላዊ ፓርቲ ለመመስረት ውህደቱ ወቅታዊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

 ዓለምነው መኮንን

ነጋሽ መሐመድ

ሸዋዬ ለገሠ