«የአዲስ አበባ ባላደራ» መግለጫ
ዓርብ፣ መስከረም 30 2012ማስታወቂያ
ከዚህ በፊት በተለያየ መንገድ ነገሮች እንዲስተካከሉ ብንጮህም ሰሚ በማጣታችን ሁለተኛውን የሰላማዊ ትግል ስልት ለመጠቀም ተገደናል በዚህም መፍትሄ ካላከኘን በቀጣይ መንግሥትን ወደሚያስገድዱ የሥራ ማቆም እና ሌሎች የትግል ስልቶች ለመግባት እንገደዳለሁ ብሏል። በሕጉ መሠረት ሁሉንም መስፈርት አሟልቻለሁ ያለው ባለ አደራው ምክር ቤት ከከተማ መስተዳድሩ ግን እስካሁን በአዎንታም ሆነ በአሉታ ምላሽ አልተሰጠንም ያ ማለት ሰልፉን ፈቅዷል ማለት ነው ስለዚህም በሰልፉ ላይ አስፈላጊውን ጥበቃ የማድረግ ኃላፊነት እንዳለበትም አመልክቷል። ይህ መግለጫ በሚሰጥበት ወቅት የተወሰኑ ወጣቶች መግለጫውን በመቃወም ድምጻቸውን ሲያሰሙ ነበር። ሰሎሞን ሙጬ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
ሰሎሞን ሙጬ