«የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት ባልደራስ»
ረቡዕ፣ መጋቢት 25 2011ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት ባልደራስ የተባለው ስብስብ መሪዎች ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። የአዲስ አበባ ህዝብ ጥያቄዎች መልስ እንዲያገኙ ጥሪ በቀረበበት በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ምክር ቤቱ ምንም ዓይነት የሥልጣን ጥያቄ እንደሌለው አስታውቋል። ከዚያ ይልቅ የከተማዋ ህዝብ ጥያቄዎች እንዲመለሱ የሚሰራን ፓርቲ እንደሚደግፍ ገልጿል። በሂደትም እስከ እያንዳንዱ ቀበሌ ድረስ በሚዘረጋ መዋቅር እንደሚወከልም አስታውቋል። ምክር ቤቱ ባለፈው ቅዳሜ አዲስ አበባ ራስ ሆቴል ዉስጥ ሊሰጥ የነበረዉ ጋዜጣዊ መግለጫ በፀጥታ አስከባሪዎች ተከልክሎ ነበር። መግለጫውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ወኪላችን ሰሎሞን ሙጬ ተጨማሪ ዘገባ አለው።
ሰሎሞን ሙጬ
ኂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ