1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአውሮጳ ኅብረትን ያሰጋዉ የኮሮና ተኅዋሲ

ማክሰኞ፣ የካቲት 17 2012

የኮሮና ተሐዋሲ በአውሮጳም በመስፋፋት መጀመሩ የአውሮጳ ኅብረትን እና አባል ሃገራትን እጅግ አሳስቧል። እስካሁን በጀርመን፤ ፈረንሳይ እና ብሪታንያ ተሐዋሲው ስለተገኘባቸው ጥቂት ሰዎች ከመነገሩ ባለፈ ስጋት ያልነበረው ይኽ ተሐዋሲ በአውሮጳ ስጋት ደቅኗል።

https://p.dw.com/p/3YPJO
Italien Coronavirus abgeriegelte Region bei Venedig
ምስል Getty Images/AFP/M. Sabadin

ኮሮና የአውሮጳም ስጋት?

የኮሮና ተሐዋሲ በአውሮጳም መስፋፋት መጀመሩ የአውሮጳ ኅብረትን እና አባል ሃገራትን እጅግ አሳስቧል። እስካሁን በጀርመን፤ ፈረንሳይ እና ብሪታንያ ተሐዋሲው ስለተገኘባቸው ጥቂት ሰዎች ከመነገሩ ባለፈ ስጋት ያልነበረው ይኽ ተሐዋሲ በአውሮጳ ስጋት ደቅኗል። በጣሊያን ካለፈው ዐርብ ወዲህ ብቻ 200 ሰዎች በተሐዋሲው  መያዛቸው እና ስድስት ሰዎችም መሞታቸው በኅብረቱ  ውስጥ ግዙፍ የጤና ቀውስ እንዳያስከትል አስግቷል።  ጣልያን ውስጥ 11 ከተሞች ውስጥ ሰዎች እንዳይገቡም ኾነ ከከተማዪቱ እንዳይወጡ የሀገሪቱ መንግሥት ከልክሏል። የአውሮጳ ኮሚሽን የአስቸኳይ ጊዜ ርዳታ ኮሚሽን ኮሚሽነር እና የጤና እና ምግብ ኮሚሽነር ትናንት በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።  የብራስልሱ ወኪላችን ተጨማሪ ዘገባ አለው። 

ገበያው ንጉሤ

ማንተጋፍቶት ስለሺ
ነጋሽ መሐመድ